"ጠ" እና "ፀ"

*** (ግጥም ፡ በደመቀ ከበደ)

Journalist Demeke Kebede

Journalist Demeke Kebede Source: Supplied

ታገሬ ወጥቼ - ከተማ ገብቼ

ገድ ቀናኝና - ካንቺ ተዋድጄ

አልችል ብል ልለምደው - የከተማን ኑሮ

በአነጋገሬ ላይ - አሰማሽ እሮሮ፤

‹‹ፀሐይ›› አልኩ ብዬ - ‹‹ጠሀይ›› በማለቴ

‹‹ፀጉር›› ልል ፈልጌ - ‹‹ጠጉር›› የሚልን ቃል - ከአፌ በማውጣቴ ተበሳጨሽና - ቁጣ አዘነብሽብኝ በ‹‹አድርግ››ና ‹‹አታድርግ›› - ግማሽ ቀን ዋልሽብኝ፤

 

‹‹ ‹ፀ› ማለት ሲገባህ - ‹ጠ›ን አትጥራ ሁሌ - ዳግም እንዳልሰማ እንዳታዋርደኝ እንዳታስፎግረኝ - በመሃል ፒያሳ - በነቃ ከተማ በቃህ አቁም በቃ - ዘወትር ‹ጠ› አትበል ‹ጠሎት›ንም ‹ፀሎት› - ‹ጠሀይ›ን ‹ፀሐይ› በል!››

 

ትዕዛዝሽን ላከብር - ምን ብጠነቀቅም

‹‹ጠ››ን በ‹‹ፀ›› ተክቼ - ተናግሬ አላውቅም፤

 

ይህን አየሽና…

 

‹‹ይቅር እንለያይ - በአንተ አልፈር እኔ

ከብጤህ ተዛመድ - አቻ ሽቷል ጎኔ!››

ብለሽ ተለየሽኝ - ያላንዳች ይሉኝታ

ባላወቅሁት ‹‹ቅጥበት›› - ባልገመትኩት አፍታ፤

ሳስበው አመመኝ…

ሰበብሽ ያበግናል - ያጨሳል፣ ያደብናል

ሰው እንዴት በቋንቋ - ፍቅርን ይመዝናል?

 

ታዲያ ምኔ ዋዛ - ምኔ ሞኝ ነውና

እኔም በተራዬ - እንተከተክ ጀመር - ‹‹ፀ››ን ተካሁኝና

ይኸው ይኸውና …

‹ፅፍራም› ነሽ፣ ‹ገፃፃ› - ፍቅር የማይገባሽ

‹ፀብ› እንጅ መዋደድ - ‹ፄና› የሚነሳሽ

እስኪ አሁን በሞቴ

ምኑ ነው ‹ፅፋቴ›?

በ‹ፀራራ› ፀሐይ - ‹ወክ› እናድርግ ማለቴ?

‹ፀርሙስ› ሙሉ ቢራ - በቀን ‹መፀፃቴ›?

በ‹ፀፀር› ጎዳና - ‹ፀጅ› ይዤ ‹መውፃቴ›?

ነው ወይስ ኮብልዬ - ከ‹ገፀር› ‹መምፃቴ›?

 

በያ ንገሪኛ

ምኑ ነው እሚያሳፍር - ይህ የኔ አማርኛ?

እኔ ግን ልንገርሽ?

በ‹ፀበልም› ባልድን - ባይለቀኝም ፍቅርሽ

አብሮ መውፃት መግባት - ሰርክ ካሳፈረሽ

ወይ ካሸማቀቀሽ

ከእኔ ጋር መታየት - ከሰው ካሳነሰሽ

ያውልሸ ጎዳናው - ሂጅ ወደፈለገሽ

‹ቢፄ›የን አላፃም

እኔ የሞፃው ልጅ

‹ፀብራራ›ው ‹ገፀሬ› - ‹ፃፃ› አለኝ መሰለሽ!!


Share
Published 19 December 2020 11:58am
By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service