ድሬዳዋ ቀፊራ አካባቢ የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶች እንዲወገዱ ከተደረጉበት ጉድጓድ ቆፍረው በማውጣት ሊሸጡ የነበሩ 17 ግለሰቦች በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ከተለያዩ ሱቆች ተሰብስበው ተቀብረው የነበሩት የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸው ምርቶች 1ሺ700 ሊትር የምግብ ዘይት፣ ዱቄት ወተት እና ሩዝ እንደነበሩ ተገልጧል።

Expired goods.png

Credit: Supplied

የመጠቀሚያ ግዜ ያለፈባቸው ምርቶች እንዲወገዱ ከተደረጉበት ጉድጓድድ ቆፍረው በማውጣት ለመሸጥ በመዘጋጀት ላይ የነበሩ 17 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ድሬ ፖሊስ ገለፀ።

በከተማዋ ቀፊራ እየተባለ በሚጠራው የገበያ ስፍራ በጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉና የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው ምርቶች ከተለያዩ ሸቀጣሸቀጥ ሱቆች 1ሺ700 ሊትር የምግብ ዘይት፣ ዱቄት ወተት እና ሩዝ ተለይቶ በመሰብሰብ በጉድጓድ ተቆፍሮ እንዲወገድ መደረጉን የገለፀው ፖሊስ ተከሳሾቹ ምርቱ ከተቀበረበት ጉድጓድ ቆፍረው በማውጣት ለመሸጥ በመዘጋጀት ላይ እንዳሉ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት መያዛቸውን አስታውቋል።

የአዲስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያና የመጋላ ፖሊስ ጣቢያ በጋራ በሰሩት ቅንጅታዊ ስራ ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸው 10 ሴት እና 7 ወንድተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ገልጧል።

Share
Published 4 November 2024 8:58am
Updated 4 November 2024 9:01am
By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service