የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር ደኤታ ታየ ደንደአ ታሰሩ

አቶ ታየ ደንደአ ለእሥር የበቁት ከፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በሕቡዕ ሲስሩ ተደርሶባቸዋል በሚል ተጠርጣሪነት ነው።

Taye D.png

Former state minister for peace, Taye Dendea. Credit: ENA

የቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ታየ ደንደአ በተጠርጣሪነት ለእሥር የተዳረጉት በፌዴራል የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ሲሆን፤ ግብረ ኃይሉ ታህሳስ 2 ቀን 2016 ባወጣው መግለጫ አቶ ታየ "ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሱ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በተሳሰር ለጥፋት ተልዕኮ በሕቡዕ ሲሰራ ተደርሶበታል" ብሏል።

መግለጫው አያይዞም " ተጠርጣሪዉ ታየ ደንደአ በህግ ቁጥጥር ሥር በዋለበት ወቅትም በመኖሪያ ቤቱ ዉስጥ በተደረገ ፍተሻ፤ ግለሰቡ በህቡዕ ለሚያደርገዉ ፀረ-ሰላም እንቅስቃሴ ሲገለገልባቸዉ የነበሩ የተለያዩ 9 ሞባይሎች፣ 4 ላፕቶፖች፣ 3 አይፖዶች፣ በርካታ ፍላሾች፣ 2 የፊትና የኋላ የተለያዩ ተሸከርካሪ ሰሌዳዎች እና ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች፣ ክላሽንኮቭ ጠመንጃና ሽጉጦች ከመሰል ጥይቶች ጋር እንዲሁም የኦነግ ሸኔ አርማዎችና በተለያዩ ግለሰቦች ስም የተዘጋጁ የኦነግ ሸኔ መታወቂያዎች፣ ሰነዶችና ማስታወሻዎች ተገኝተዋል" ሲል አስታውቋል።

የፌዴራል ፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ የአቶ ታየ መኖሪያ ቤት ፍተሻ በተደረገበት ወቅት በሶስት መታወቂያዎች የሚጠቀም አንድ የኦነግ ሸኔ አባል ተደብቆ መገኘቱን የገለጠ ሲሆን፤ በመንግሥትና በፖርቲ መዋቅር ዉስጥ ሆነዉ በተመሳሳይ ድርጊት በተሰማሩ አካላት ላይም ግብረ ኃይሉ ክትትል በማድረግ ላይ እንደሆነና ውጤቱንም ለሕዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አክሎ ገልጧል።




Share
Published 13 December 2023 8:21am
By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service