በኮቪድ-19 እና የፈንጣጣ ሉላዊ ወረርሽኝ ላይ ተደራቢ አዲስ "ላንግያ" ቫይረስ ተከሰተ

የደቡብ ኮሪያ የተቃውሞ ሰልፈኞች አገራቸው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ያላትን ወታደራዊ ትብብር እንድታቋረጥ ጠየቁ

More pandemics will follow after COVID-19.jpg

Health experts are warning more pandemics will follow after COVID-19. Credit: AAP / Darren England

ዳግም አገርሽቶ ባለው ኮቪድ - 19 እና በመዛመት ላይ በሚገኘው ሉላዊ የዝንጀሮ ፈንጣጣ ላይ አዲስ ላንግያ ቫይረስ ቻይና ውስጥ ተከስቷል።

በዚህ ወር ሳይንቲስቶች በኒው ኢንግላንድ የሕክምና ጆርናል ጥናታዊ ፅሁፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት ላንግያ ቫይረስ ቻይና ውስጥ መከሰቱን አስፍረዋል።

ሆኖም እስካሁን ድረስ በአዲሱ ላንግያ ቫይረስ ሳቢያ የተመዘገበ ሞት የለም። ቫይረሱም ከሰው ወደ ሰው ይተላለፍ አይተላለፍ አልታወቀም።

አንድ የዋይት ሃውስ ሰነድ ሉላዊ የቫይረስ መስፋፋት መጠን እየናረ እንደሚሔድ አመልክቷል።

ከእንሰሳት ተላላፊ የሆኑ በሽታዎች በሕዝብ ቁጥር እያደገ መሔድ፣ የአየር ንብረት ለውጥና የሰዎች ባህሪይን ለሉላዊ ወረርሽኝ ተዛማችነት በሁነኛ አስባብነትም ጠቅሷል።

***
በደቡብ ኮሪያ መዲና ሶል በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሰልፈኞች የደቡብ ኮሪያ መንግሥት በሰሜን ኮሪያና ቻይና ላይ ይዞት ያለውን ውጥረት ፈጣሪ አቋምና ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር የሚያካሒደውን ወታደራዊ የጋራ ጦር ልምምድ እንዲገታ እንፈልጋለን ሲሉ ጥሪ አቀረቡ።

የተቃውሞ ሰልፈኞቹ የደቡብ ኮሪያ መንግሥት ከዋሽንግተን ጋር ያለውን ወታደራዊ ትብብር አቋርጦ ከፒዮንግ ያንግ ጋር የሰላም ስምምነት ውልና ትብብር እንዲያበጅ ጠይቀዋል።

የተቃውሞ ሰልፉ የተካሔደው ከፕሬዚደንቱ ጽሕፈት ቤት ሁለት ኪሎ ሜትር ተኩል ርቀት ላይ ከሚገኘው ታሪካዊው ናምዳእሙን በር ላይ ነው።

ከተቃውሞ ሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል አንዱ የሆኑት ቾይ ኡን ሲናገሩ፤

"የዩን ሱክ አስተዳደር ስልጣን ከያዘ አንስቶ ደቡብ ኮሪያ በሰሜን ኮሪያና ቻይና ላይ አክራሪ ፖሊሲ ይዛለች። እኛ ዛሬ እዚህ የተገኘነው በኮሪያ ባህረ ሰላጤ ሰላም እንዲሰፍንና ለኮሪያውያን ዕርቅና ትብብር ጥሪ ለማድረግ ነው" ብለዋል።





Share
Published 14 August 2022 10:40am
Updated 14 August 2022 10:43am
By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service