የጃፓኑ ዶዳይ ኩባንያ በኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሞተር ሳይክሎችና ባትሪ መለዋወጫ ጣቢያዎች ልገነባ ነው

ኩባንያው በመጪው አንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ 5,000 በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ሞተር ሳይክሎችና 100 የባትሪ መለዋወጫ ጣቢያዎች እንደሚገነባ አስታውቋል፡፡

Ethio Japan 1.png

Credit: Suplied

ዶዳይ ፋብሪካ የሚገነባቸው የባትሪ መለዋወጫ ጣቢያዎች የሞተር ባለቤቶች ሙሌት ተደርጎ የተጠቀሙት ባትሪን ለኩባንያው ሰጥተው ሙሌት የተደረገ ባትሪ የሚወስዱባቸው ጣቢያዎች መሆናቸው ተነግሯል፡፡

በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የሞተር ብስክሌቶችን እና የባትሪ መለዋወጫ ጣቢያዎች በኢትዮጵያ ማምረት መጀመሩን የተናገረው የጃፓኑ ዶዳይ ኩባንያ ይህንኑ ለማቀላጠፍ የመንግሥት የልማት ድርጀቶች የበላይ ከሆነው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና ዶዳይ ማኑፋክቸርንግ በተፈራረመት የመግባቢያ ስምምነት መሰረት በመጪ አንድ ዓመት ውስጥ 100 የባትሪ መለዋወጫ ጣቢያ የሚገነባ ይሆናል፡፡
Ethio Japan 2.png
የባትሪ መለዋወጫ ጣቢያ መገንቢያ ቦታዎችን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ያቀርባል፡፡

ወደፊት የመግባቢያ ስምምነቱ ዝርዝር ይፋ እንደሚሆንም ተገልጧል።

የኤሌክትሪክ ሞተር ሳይክሎችን የሚያመርተው ዶዳይ ኩባንያ ፉብሪካውን በአዲስ አበባ ጎተራ የተከለ ሲሆን ለዚህም 7 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት ማድረጉን አስታውቋል፡፡




Share
Published 24 October 2024 3:31pm
By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service