የድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ የቀብር ሥነ ሥርዓት ሐሙስ ለፈፀም ነው

የድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ የቀብር ሥነ ሥርዓት የሚፈፀመው ሐሙስ መስከረም 19 ቀን 2015 አራት ኪሎ በሚገኘው ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል መሆኑ ተገልጿል።

Singer Madingo Afework.jpg

Singer Madingo Afework. Credit: PR

ለማዲንጎ የቀብር ሥነ ሥርዓት የተቋቋመው ኮሚቴ ቃል አቀባይና የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ ሰይፉ ፋንታ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ ፕሮግራም መግለጡን አዲስ ማለዳ በረቡዕ እትሙ አመልክቷል። 

በዚሁም መሠረት ከቀብር ሥነ ሥር ዓቱ በፊት የሽኝት ፕሮግራም ይካሔዳል፤ ዝርዝር መርሃ ግብሩም በቀጣይነት እንደሚነገር ተጠቅሷል።  

ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ ትናንት ማክሰኞ መስከረም 17 ቀን 2015 ከጠዋቱ 1:30 አክባቢ ለሀኪሙ ስልክ በመደወል ወደ ክሊኒከ እንደሔደና ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በሚገኝ አንድ የግል ክሊኒክ የሕመም ማስታገሻዎችንና ሌሎች መድኃኒቶችን ወስዶ እንደነበር የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። 

የማዲንጎ ሕይወትም ከቀትር በኋላ ከረፋዱ 3 : 00 ሰዓት አካባቢ ማለፉ ተገልጧል።    
የድምፃዊ አስከሬን ሕይወቱ ካለፈበት የግል ክሊኒክ ወደ አቤት ሆስፒታል ተወስዶ ምርመራ እየተካሔደ መሆኑን የገለጠው ፖሊስ በቀረበለት አቤቱታ መሠረት የድምፃዊውን ይውሞት መንስዔ ለማጣራት የአስከሬን ምርመራ ውጤቱን እየተጠባበቀ መሆኑን አስታውቋል። 
 
አዘዞ ተወልዶ በደብረ ታቦር ከተማ ታደገውና ከ19880ዎቹ አጋማሽ አንስቶ የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ ከተቀላቀሉ ድምፃውያን መካከል በቀዳሚነት የሚጠቀሰው ማዲንጎ አፈውርቅ፤ በ1987 "ስያሜ አጣሁላት" በተሰኘው ቀዳሚ የልበም ሥራው ከሙዚቃ አፍቃሪያን ጋር ተዋውቋል። 

በ1990ዎቹ "አይደረግም" እና ከቅርብ ዓመታት በፊት "ስወዳት" የተሰኙ ተወዳጅነት ያስገኙለትን የሙዚቃ አልበሞችን ለአድማጮቹ አበርክቷል።  
ድምፃው ማዲንጎ ለሕልፈተ ሕይወት ከመብቃቱ በፊት አራተኛ አልበሙን ለአድማጮች ለማቅረብ በመሥራት ላይ ነበር።
 

Share
Published 28 September 2022 7:09pm
Updated 28 September 2022 7:16pm
By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service