ቪክቶሪያ የነርስና አዋላጅነት ተማሪዎችን በመንግሥት ክፍያ በነፃ ልታስተምር ነው

የቪክቶሪያን የሕክምና ሥርዓት ለመታደግ የቪክቶሪያ መንግሥት ከ10,000 በላይ ለሆኑ የዩኒቨርሲቲ ዲግሪዎቻቸውን በነርስና አዋላጅነት ኮርስ ለመውሰድ ለሚሹ ተማሪዎች ሙሉ ክፍያ ከፍሎ ለማስተማር ማቀዱን አስታወቀ

Victorian Premier Daniel Andrews.jpg

Victorian Premier Daniel Andrews. Credit: Darrian Traynor/Getty Images

ወደ ዩኒቨርስቲ ዘልቀው የነርስና አዋላጅነት ኮርስ ለመውሰድ ለሚሹ ተማሪዎች ተነሳሽነቱን የወሰደው የቪክቶሪያ መንግሥት $270 ሚሊየን ዶላርስ መበጀቱን ያስታወቀው ዛሬ እሑድ ኦገስት 28 ነው።

ከአምስት ዓመት በታች ጊዜ ውስጥ በተነደፈው ፕሮግራም መሠረት በ2023 እና 2024 ለተመዘገቡ ተማሪዎች እስከ $16,500 የሚደርስ በነፃ ትምህርት ዕድል ኮርስ ወጪዎቻቸው ይሸፈናሉ።

ተማሪዎች በሶስት ዓመት የትምህርት ጊዜያቸው $9000 የሚያገኙ ሲሆን፤ ለሁለት ዓመታት በቪክቶሪያ የሕዝብ ጤና አገልግሎቶች ውስጥ ተቀጥረው ከሠሩ ቀሪው $7500 የሚከፈላቸው ይሆናል።

እንዲሁም የድኅረ ነርስ ስልጠናቸውን በከፍተኛ ክብካቤ፣ ድንገተኛ፣ የሕፃናትና ካንሰር ክብካቤዎች አካባቢ ለሚወስዱ በሺህዎች ለሚቆጠሩ ተማሪዎች በአማካይ $10,000 ይሰጣል።

Share
Published 28 August 2022 8:15pm
By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service