"ከአዝማሪና" እስከ "ትዝታ ንግሥና"፤ ዝነኛው አንጋፋ ድምፃዊ ጌታቸው ካሣ ከእዚህ ዓለም በሞት ተለየ

Getachew Kassa.jpg

Singer Getachew Kassa. Credit: PR

ድምፃዊ ጌታቸው ካሣ ከ SBS አማርኛ ሬዲዮ ጋር በሕይወ ሳለ ባካሔደው ቃለ ምልልስ ስለ ሙዚቃ ሕይወት ጉዞው አውግቷል።


አንኳሮች
  • አዝማሪና የሙዚቃ ፍቅር
  • ከሸክላ አድማጭነት ወደ መድረክ ባለቤትነት
  • ከስደት ወደ አገር ቤት
አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሣ በ'የካቲት 12' ሆስፒታል ሕክምና ሲከታተል ቆይቶ ትናንት ለሊት ሕይወቱ አልፏል።

ድምፃዊ ጌታቸው በ1960ዎቹ እና 1970ዎቹ በኢትዮጵያ በበርካታ ትላልቅ የሙዚቃ ክለቦች በመስራት ታዋቂነትን ማትረፍ ችሎ ነበር።

ጌታቸው ከሙዚቃ ሥራዎቹ ውስጥ "ብርቱካን ነሽ ሎሚ፣ ሀገሬን አትንኳት፣ ውብ አዲስ አበባ፣ ሳይሽ እሳሳለሁ፣ የከረመ ፍቅር" እና በሌሎች በርካታ ዘፈኖቹ ከፍ ያለ አድናቆትና ዕውቅናን አግኝቶባቸዋል።

አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሳ ሙዚቃን ከ 6 አመቱ ጀምሮ የተጫወተ ሲሆን በፈጣን ባንድ ፣ ሸበሌ ባንድ ፣ የቬነስ ባንድ እና በኋላም ከዋልያስ ባንድ ጋር በመሆን የተለያዩ ይዘት ያላቸውን የሙዚቃ ስራዎችን ተጫውቷል።

ጌታቸው “ትዝታ እና ፈጣን” በሚባል የሙዚቃ ስልቶች ተወዳጅ የነበረ ሲሆን ከተጫወታቸው ተወዳጅ ዜማዎች መሃከል "ሀገሬን አትንኳት "፣ አዲስ አበባ" ፣ “ትዝ ባለኝ ግዜ”፣ "የከረመ ፍቅር” ፣ “መሄዴ ነው" ፣ "ሳይሽ እሳሳለሁ" የተሰኙት የሚጠቀሱ ናቸው።

Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service