"የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የተሃድሶና ተስፋ ዘመን ነው፤ መልካም አዲስ ዓመት" የአውስትራሊያ ፌዴራል ተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን

Leader of the Opposition Peter Dutton MP.jpg

Leader of the Opposition Peter Dutton MP. Credit: AAP Image/Lukas Coch

ከእንግሊዟ ዳግማዊት ኤልሳቤጥ ሕልፈተ ሕይወት ጋር ተጋጥጥሞ እ.አ.አ. ከ2011 ጀምሮ ያልተቋረጠውን የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትሮች የኢትዮጵያን አዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ በዘንድሮው ዓመት ይዘን ባንቀርብም፤ የተቃዋሚ ቡድን መሪዎች የአዲስ ዓመት መልዕክት ግና አልተስተጓጎለም። ከንግሥቲቱ ሕልፈተ ሕይወት ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ መቅረጽ የተቻለውን የአውስትራሊያ ሊብራል ፓርቲና የፌዴራል ተቃዋሚ ቡድን መሪ የአዲስ ዓመት መልዕክት ማሰናዳት ችለናል። እነሆን።


በሊብራል ፓርቲና እንደ ተቃዋሚ ቡድን መሪነቴ መልካም የኢትዮጵያ አዲስ ዓመትን እመኝላችኋለሁ።

ለአውስትራሊያውያን - ኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ፣

አውስትራሊያ ውስጥ የትም ሁኑ የት፤ አዲሱን ዓመት ዘላቂ ሥርዓተ ወጎች በሆኑት በፀሎት፣ ከቤተሰብ በመጣ መልዕክት፣ ከወዳጆች ጋር ሆኖ በማክበር፣ ችቦ በመለኮስ፣ ምናልባትም አረቄ በመጎንጨት ትቀበሉታላችሁ።

ምንም ጥርጣሬ የለውም፤ ስለ ዕንቁጣጣሽ አመጣጥ አፈ ታሪክ መነገሩም አይቀርም።

ንግሥተ ሳባ ንጉሥ ሰለሞንን ጎብኝታ ወደ አገር ቤት ስትመለስ እንደምን ዕንቁ ይዛ እንደመጣች።

ንግሥቲቱ በጉዞዋ እንደከበረች ሁሉ፤ አውስትራሊያም እዚህች ታላቅ አገራችን ላይ በፍልሰትም ይሁን በስደተኝነት በሠፈሩት ኢትዮጵያውያን ከብራለች።

ከ1960ዎቹ ወዲህ በበርካታ ምክንያቶች ወደ አውስትራሊያ መጥተዋል።

ከጭቆና ለመሸሽ፣ የተፈጥሮ አደጋን ለማምለጥ፣ መልካም ዕድሎችን ፍለጋና ከቤተሰብ ጋር ለመቀላቀል።

ምክንያቶቹ ምንም ይሁኑ ምን፤ ምድራችንን የረገጡ ኢትዮጵያውያን ታትረው ሠረተዋል፤ የአውስትራሊያን የሕይወት ዘዬ ተቀብለዋል፣ እንዲሁም፤ እንደ አገር አዋድዶ ያያያዙንን ዲሞክራሲያዊ ዕሴቶች በእጅጉ ተከባክበው ይዘዋል።

ንግሥቲቱ [ንግሥተ ሳባ] በጉዞዋ እንደከበረች ሁሉ፤ አውስትራሊያም እዚህች ታላቅ አገራችን ላይ በፍልሰትም ይሁን በስደተኝነት በሠፈሩት ኢትዮጵያውያን ከብራለች።
የተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን

14 ሺህ ያህል የኢትዮጵያውያን ማኅበረሰብ አባላት በየዓመቱ ለሕብረተሰባችን ሁነኛ አስተዋፅዖዎችን ያበረክታሉ።

እያንዳንዳቸውን ስለ አይበገሬነታቸውና አበርክቶዎቻቸው አመሰግናለሁ።

የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት የተሃድሶና ተስፋ ዘመን ነው።

እናም፤ ለአውስትራሊያውያን - ኢትዮጵያውያን በመጪው አዲስ ዓመት መልካም ዕድሎችንና ጤናን እመኛለሁ።

መልካም አዲስ ዓመት

በጣም አመሰግናለሁ።

Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service