"ሁላችንም ኢትዮጵያውያን የምንፈልገው አሸናፊ መሆንን ነው፤ በጋራ የምናሸንፈበትን ሰላም ለማግኘት ዋጋ መክፈል ይኖርብናል" ሰብለወርቅ ታደሰ

Seblework.jpg

Seblework Tadesse. Source: SBS / S.Tadesse

አቶ ልዑል ፍሰሃ - በሜልተን ክፍለ ከተማ የሥራ ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ፣ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ - በብሪስበን - ኩዊንስላንድ የደቡብ ማኅበረሰብ ማዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ - በቪክቶሪያ AMES የሠፈራ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅና ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ጥናት ተመራማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ስላለው የሰላም ድርድር አስፈላጊነት ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • የድርድር ስኬት ምልከታ
  • የተደራዳሪዎች ሚና
  • ተስፋና ስጋት
“ተደራዳሪዎች ግጭቱ ሁሉንም የሚጎዳ መሆኑን በመቀበል፣ ግጭቱን በመነጋገር መፍታት እንችላለን የሚል በጎ መንፈስን በቀዳሚነት ካስቀመጡ የድርድሩ የመሳካት ዕድል ሰፊ ይሆናል ብዬ አስባለሁ። በጥንቃቄ ከተደማመጡም መልካም ዕድሎች ይኖራሉ።” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

***

“የችግሩ ምንጭ ፖለቲካው እንደመሆኑ፤ መፍትሔው ያለው ፖለቲካው ላይ ነው።” ዶ/ር ተበጀ ሞላ

***

“የፌዴራሉ መንግሥት የሚፈልገውና በተለይም የአማራ ክልል መንግሥት ፍላጎት የተለያየ ነው። ያ አንድ ሳይሆን፤ የሰላም ዝግጁነት ሳይፈጠር የሰላም ድርድር ለማድረግ ሌላ ችግር ይፈጥራል የሚል ስጋት አለኝ” አቶ ልዑል ፍሰሃ


Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service