በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ያለው የሰላም ድርድር ለስኬት እንዲበቃ የሕዝብና የባሕር ማዶ ኢትዮጵያውያን ሚና ምን ሊሆን ይገባል?

Ehiopian Diaspora community.jpg

Tigrayan Community in South Africa (L), and Ethiopian Community in Israel (R). Source: Getty / Alet Pretorius / Menahem Kahana

አቶ ልዑል ፍሰሃ - በሜልተን ክፍለ ከተማ የሥራ ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ፣ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ - በብሪስበን - ኩዊንስላንድ የደቡብ ማኅበረሰብ ማዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ - በቪክቶሪያ AMES የሠፈራ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅና ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ጥናት ተመራማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ስላለው የሰላም ድርድር አስፈላጊነት ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • ብሔራዊ ጥቅምና የሰላም ተደራዳሪዎች
  • ለሰላም ስኬት ሕዝባዊ ተፅዕኖዎች
  • የባሕር ማዶ ነዋሪ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሚና
“ሁልጊዜ ጦርነትን የሚጀምሩት ፖለቲከኞችና የጦር ጠበብቶች ናቸው። ሕዝብ እንደ ሕዝብ ሰላምን ይፈልጋል። ለሰላም የሚደረገው ማንኛውም ርብርብ በሁሉም ወገን ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል። በዳያስፖራውም ጭምር፤ ነገር ግን የሰላም ንግግሩ እውነተኛ መሆንና ሕዝብን ያቀፈ መሆን አለበት።” አቶ ልዑል ፍሰሃ

***

“ችግሩን ከምናባብሰው አካል አንዱ ስለሆንን፤ ችግሩ እንዲበርድም ለማድረግ በውጭ የምንንኖር ኢትዮጵያውያን በሙሉ ሚና ሊሆን ይገባል። ይኼ ድርድር ውጤታማ እንዲሆን እያመመንም ጭምር አሉታዊ ነገሮችን ባለማራገብ፤ ከልዩነቶቻችን ይልቅ አንድነታችን ላይ መሥራት የምንችልበት ዕድል ቢኖር ኢትዮጵያ አትራፊ ትሆናለች።” ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ

***

“ያለፉ አሉታዊ ነገሮች ላይ ከማተኮር ይልቅ የሚመጣው ተስፋ ላይ ከተተኮረ ችግሩ ይፈታል ብዬ አስባለሁ። ሁሉም የሰላም አምባሳደር ከሆነ የጦርነት ድምፆች ይቀንሳሉ። የሰላም መንገዶች ይጨምራሉ ብዬ አስባለሁ።” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

***
"ከተቻለ ገንቢ ምክረ ሃሳብ ማቅረብ፤ ካልተቻለ አላስፈላጊ ተፅዕኖ ፈጥሮ ውይይቱ ዕንቅፋት እንዳይገጥመው ማድረግ።" ዶ/ር ተበጀ ሞላ

Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service