“የሰላም ድርድሩ ቢሳካ ወይም ጎጂ ጎን ቢገጥመው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጥሩ ልምዶችን ያገኛል ብዬ አስባለሁ” ዶ/ር ተበጀ ሞላ

Dr. T Molla.jpg

Dr Tebeje Molla. Source: SBS / T.Molla

አቶ ልዑል ፍሰሃ - በሜልተን ክፍለ ከተማ የሥራ ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ፣ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ - በብሪስበን - ኩዊንስላንድ የደቡብ ማኅበረሰብ ማዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ - በቪክቶሪያ AMES የሠፈራ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅና ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ጥናት ተመራማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ስላለው የሰላም ድርድር አስፈላጊነት ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • የሰላም ድርድርና የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን
  • ልምድ ቀሰማ
  • አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖዎች
“አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው መንግሥት የደካማ ኃይሎች ስብስብ ስለሆነ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ፈርጥ የሆነ ጥሩ ሃሳብ ቢያቀርብላቸውም የመወሰን አቅማቸው ውስን ነው።” አቶ ልዑል ፍሰሃ

***

“በኢትዮጵያና መንግሥትና ሕወሓት መካከል የሚካሔደው ድርድር በሰላም ቢያልቅ ለኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ትልቅ ግብኣት ይሆናል። አገራዊ ምክክሩ ሁላችንም ሰጥተን የምንቀበልበት መደረክ ነው፤ ድርድሩ ካልተሳካ በአገራዊ ምክክሩ ላይ ጥላ ያጠላል ብዬ ነው የማስበው።” ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ

***

“ድርድሩ ከተሳካ በሰላማዊ መንገድ ተወያይተን ችግሮችን መፍታት እንድንችል ትምህርት ይሰጠናል፤ ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዕድል ይከፍታል ብዬ አስባለሁ። ኦሮሚያ ውስጥ ጠብመንጃ አንስቶ የሚዋጋ ስላለ ከእነዚያም ጋር ከጠብመንጃ ይልቅ በሰላማዊ መንገድ ተነጋግሮ ወደ አገራዊ ጉዳይ የማምጣትና አብሮ የመሥራት ዕድል ይፈጥራል ። በአገራዊ ምክክሩ የመሳተፍ ዕድልም ይጨምራል።” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

***

Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service