ለሰላም ድርድር ስኬት የአደራዳሪዎች አዎንታዊና አሉታዊ ሚና ይሆናል?

Chief Olusegun Obasanjo.jpg

High representative of the African union for the horn of Africa and former Nigerian President Olusegun Obasanjo. Source: Getty / Anadolu Agency/Anadolu Agency via Getty Images

አቶ ልዑል ፍሰሃ - በሜልተን ክፍለ ከተማ የሥራ ስልጠና ከፍተኛ ባለሙያ፣ ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ - በብሪስበን - ኩዊንስላንድ የደቡብ ማኅበረሰብ ማዕከል ማኔጂንግ ዳይሬክተር፣ አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ - በቪክቶሪያ AMES የሠፈራ ጉዳይ ሥራ አስኪያጅና ዶ/ር ተበጀ ሞላ - በዲከን ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ፖሊሲና የማኅበራዊ ፍትሕ ጥናት ተመራማሪ፤ በኢትዮጵያ መንግሥትና በሕወሓት መካከል ሊካሔድ በዕሳቤ ስላለው የሰላም ድርድር አስፈላጊነት ግለ አተያያቸውን ያጋራሉ።


አንኳሮች
  • አደራዳሪዎች
  • ገለልተኛነት
  • ተቀባይነት
“ምዕራባውያን በተለይ በአገራችን ጉዳይ እጃቸውን በግልፅ እያስገቡ ነው ያሉት። እነሱ ያጣሉናል፤ እነሱ ልናስታርቃችሁ እንምጣ ይላሉ። መፍትሔ የሚሆነው እሱ አይደለም። መፍትሔ የሚሆነው ባለፉት 20 ወራት በሕዝባችን ላይ የደረሰውን ግፍ፣ ሰቆቃና የኢኮኖሚ ውድቀት ተረድተን ከዚህ በኋላ ቢያንስ ያ ነገር እንዳይቀጥል ተመሳሳይ አቋም ልንይዝ ይገባል።” አቶ ልዑል ፍሰሃ

***
“ባለፉት 20 ወራት ብቻ ሳይሆን ለ30 ዓመታት ኢትዮጵያ በታሪኳ ሆኖባት በማያውቀው መልኩ መፈንጫ ነበረች ብዬ ነው የማስበው። እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ። ይካሔዳል ለሚባለው ድርድር ቢያንስ አደራዳሪዎቹ ከነጮቹ ይልቅ አፍሪካውያን መሆናቸው የተሻለ ሊሆን ይችላል” ወ/ሮ ሰብለወርቅ ታደሰ

***

“አደራዳሪዎቹ ምን ይሁኑ ምን ሁለቱ አካላት ከተቀበሏቸው ብዙም አስቸጋሪ ይሆናል ብዬ አላስብም። ዋናው አደራዳሪዎቹ ብቃት ያላቸው፣ ገለልተኛና የጥቅም ግጭት የሌላቸው መሆኑ ነው።” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

***

“አደራዳሪዎቹ ምን ይሁኑ ምን ሁለቱ አካላት ከተቀበሏቸው ብዙም አስቸጋሪ ይሆናል ብዬ አላስብም። ዋናው አደራዳሪዎቹ ብቃት ያላቸው፣ ገለልተኛና የጥቅም ግጭት የሌላቸው መሆኑ ነው።” አቶ ዳባሳ ዋቅጅራ

***

“ዋናው ቁልፉ ጥያቄ መሆን ያለበት ሁሉም ወገኖች በኢትዮጵያዊነትና በአገሪቱ ህልውና ላይ ያምናሉ ወይ ነው።” ዶ/ር ተበጀ ሞላ

Share
Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service